የወረዳው አስተዳዳሪ መልእክት
ውድ የዚህ ገጽ ተከታታዮች ሰላምና መልካም አስተዳደር የዘላቂ ልማት እና የማህበረሰብ ደህንነት መሰረት ናቸው። የላይ ጋይንት ወረዳ መንግስት ሰላም የሰፈነባት ውይይትና መከባበር የሰፈነበት ወረዳ ለመፍጠር ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነው። የወረዳችንን ሰላምና መልካም አስተዳደር ለማስፈን እና ለሁሉም ዜጎች ያለ አድሎ ፍትሃዊ አገልግሎት በመስጠት ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ለማረጋገጥ የጋራ ጥረታችን ይሁን።
አቶ ግርማ ይስማው
የላይ ጋይንት ወረዳ አስተዳዳሪ
ለአዲሱ ዓመት መልካም ምኞት መልእክት
እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ፡፡ ለመላው ህብረተሰባችን መልካም አዲስ አመት እንዲሆንልን በላይ ጋይንት ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ስም ከልብ እመኛለሁ! ይህንን አዲስ ዓመት ስንጀምር በምናደርገው እንቅስቃሴ ሁሉ ሰላምን፣ አንድነትን እና መከባበርን እናስቀድም።
አዲሱ አመት ለመልካም አስተዳደር፣ለተጠያቂነት እና ለህዝባችን አገልግሎት ቃላችንን የምናድስበት ወቅት ነው። በጋራ ጥረት እና ትብብር፣ የበለጠ ጠንካራ፣ የበለጠ የበለጸገ እና ሁሉንም ያካተተ ማህበረሰብ መገንባት እንችል ዘንድ ቁርጠኞች እንሁን።
ለህብረተሰባችን ብሩህ ተስፋ!! መልካም አዲስ ዓመት!
አቶ አሻግሬ አለምነው
የላይ ጋይንት ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ
የላይ ጋይንት ወረዳ አስተዳደር በ2017 ዓ.ም የክረምት ወራት ለትምህርትና ለቤት እድሳት ቁሳቁስ ድጋፍ መር-ግብር





"የአይሲቲ አቅም ግንባታ ለሁሉ !!"
ለዛሬው በቴክኖሎጂ ለሚመራው ዓለም እያንዳንዱ ዜጋ አስፈላጊ የሆኑ ዲጂታል ክህሎት ሊኖረው ይገባል። የስልጠና ፕሮግራሙ በኮምፒዩተር፣ በይነመረብ እና ዲጂታል መሳሪያዎች ላይ የንድፈ ሀሳብና ተግባራዊ ስልጠና ያካተተ ነው። ዲጂታል ማንበብና መጻፍን በማጎልበት፣ ሰልጣኞች በትምህርት፣ በሥራ እና በማህበረሰብ ልማት በልበ ሙሉነት እንዲሳተፉ ያስችላቸዋል።

በአይሲቲ መምህራንን ማብቃት!!
የላይ ጋይንት ወረዳ አይሲቲ የስራ ቡድን በ2018 በጀት ዓመት በክረምት ለመምህራንና ቀበሌ ሥራ አስኪያጆች የመሰረታዊ ኮምፒውተር ስልጠና ሰጠ።

በ2017 ዓ.ም በላይ ጋይንት ወረዳ የሰሮ ቀበሌ የአሬሮ ወንዝ ላይ የእግረኛ ድልድይ በተሳካ ሁኔታ ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።



በክልሉ መንግስት በጀት በደቡብ ጎንደር ዞን ላይ ጋይንት ወረዳ በተንጣለለው ሲናቆ ወንዝ ላይ የተገነባው 40 ሜትር ቦክስ ገርደር ኮንክሪት ድልድይ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።













